top of page
Search

የትኛው ውሻ ነህ?

Writer's picture: Mulualem GetachewMulualem Getachew



ማርከስ አርሊየስ እንደ ዘራያዕቆብ ፋላስፋው ንጉስ ተብሎ ይጠራል። በየቀኑ የጻፈው ሪፍሌክሽን “Meditation” በሚል ርዕስ ከሞተ በኋላ ሰዎች አግኝተው መጽሐፍ አድርገው አትመውታል። ይሄ መጽሐፍ ንጉስ ማርከስ አርሊየስ ከራሱ ጋር ያደረገው ንግግርን በየቀኑ የጻፈበት ነበር። ይታተማል ብሎ አንድ ቀንም አላሰበም። ይሄው ግን ለ3 ሺ ዓመታት ምርጥ መጽሐፍ ሆኗል።



ማርከስ ሰውን ከጋሪ ጀርባ እንደታሰረ ውሻ ይመስለዋል። ሕይወታ ጋሪ ናት። ውሻው ከዚህ ከሚሮጥ የሕይወት ጋሪ ጀርባ ታስሯል። የውሻው ምርጫ ሁለት ነው። ከጋሪው ጋር መሮጥ ወይም በጋሪው እየተጎተተ እና አፈር ላይ እየተንከባለለ ቆሳስሎ መንፋቀቅ። ምክንያቱም ከጋሪው ጋር በጠንካራ ገመድ ታስሯል። በመጨረሻ ውሻው ቢሮጥም ቢንፋቀቅም ደክሞት ይሞታል። ነገር ግን ከጋሪው ጋር ቢሮጥ ቢያንስ ሳይቆስል እና ሳይሰቃይ ይሞታል። በጋሪው እየተጎተተ እና አሮጥም ብሎ እየተንፋቀቀ ከሆነ ግን ሞቱን ማፋጠን ብቻ አይደለም ፥ አጭሯም ሕይወቱ የስቃይ ናት የምትሆነው።



 በተመሳሳይ አንዳንድ ሰዎች በሕይወት መቀየር በማይችሉት ነገር ሲጨነቁ ጊዜያቸውን ያባክናሉ። የዛሬውን እና የወደፊቱን ከማሰብ ይልቅ ፥ ትላንት እንዲህ ባደርግ ወይም እንዲህ ባላደርግ በማለት ምንም መለወጥ በማይችሉት ነገር በመጨነቅ ራሳቸውን ለብስጭት፣ ለጭንቀት እና ለሕመም ይዳርጋሉ። “መተው” የሚለው ጥበብ የሌላቸው ፥ ከሕይወት ጋር ወደፊት የመጓዝ ብልሃት ያልገባቸው ምስኪኖች ናቸው።



በምንም መስፈርት ብትመዝኑት ይሄ ሕይወት ያልቃል። በምንም መስፈርት ብትመዝኑት ሞት ይገታዋል። ሕይወት ደግሞ ይቀጥላል። የዓየር ንብረቱም ተለውጦ ቢሆን፣ በሙቀት እየሞትን፣ በጎርፍ እየተጥለቀለቅንም ሕይወት ይቀጥላል። ምርጫው ማርከስ እንዳለው በግድ የሚጎተት ውሻ ወይም እስከቻለው ድረስ ከሕይወት ጋሪ ጋር የሚሮጥ መሆን ነው። ሕይወት ለእኛ ስሜት እምብዛም ግድ የላትም። በተዋቀረው የተፈጥሮ ዑደት ነገሮች እርስ በእርሳቸው ባላንስ እየተደራረጉ ይቀጥላሉ። በዚህ ኃይል እና ፍጹም ጉዙፍ በሆነው የተፈጥሮ ዑደት ፊት ከትንኝ ያነሰ ቦታ ያለን ነን። ግን የገዘፈ ሥራ ሠርተን፤ ቢያንስ ግን መረዳት በምንችለው መጠን ሕይወትን ተገንዝበን ልናልፍ እንችላለን። ያ የሚሆነው ግን ክፍት አዕምሮ ሲኖረን እና ወደ ፊት ለመጓዝ፣ ለዚህ ተፈጥሮአዊ የማይደገም የየቀን አዲስ ልምድ ራሳችንን ስናሰምር ነው። አለዛም ሕይወት ግን ይቀጥላል። እኛም ተንፏቃቂ ውሻ ሆነን እንቀጥላለን።



ማርከስ በዚው መጽሐፉ ላይ ሕይወት ወንዝ ነው ይላል። “አንድን ወንዝ ሁለቴ አትረግጠውም” ይላል። ምክንያቱም ወንዝ ሁልጊዜ ወደፊት መፍሰስ ነው። ልክ እንደ ወንዝ የትላንት ሕይወታችንን መመለስ ፈጽሞ አንችልም። ብቸኛው የምንችለው ዛሬን ከትላንት በተለየ መኖር ነው። ልክ ከጋሪው ጋር እንደታሰረው ውሻ ያለን ምርጫ ሁለት ነው። ያለፈውን እየረሳን ቅዱስ ጳውሎስ ለፉልጵስዩስ ሰዎች እንዳለው (ምዕ 3 ፥ 13) “በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ” ዛሬ ላይ እና ነገ የሚገጥመንን ለመዋጀት መሮጥ ወይም ለሕይወት ሩጫ እንቢ ብሎ እየቆሰሉ እና እየተንፋቀቁ ሞታችንን ማፋጠን። እኔ እና ቤቴ የሚሻለውን መርጠናል እንዳለው ኢያሱ ፥ የኔ ምርጫ እየተንፋቀቁ ይሄን ሕይወት የበለጠ አክብዶ በማማረር እና በቁጭት ኖሮ ከመሞት ከሕይወት ማዕበል ጋር በመተባበር ወደፊት መፍሰስ ነው። የሆንኩትን እየተቀበልኩኝ ፥ አዲሱን የማይታወቀውን በጥበብ እና በማስተዋል በመጋፈጥ መኖር ነው።

318 views1 comment

Recent Posts

See All

የሰንበት ዕይታ - 16

እንቢ ማለትን በምግብ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አከራካሪ ከሆኑ ነገሮች አንዱ እና የተለያዩ ሊቃውንትም ግራ ከሚጋቡበት ነገሮች ውስጥ ንጹሁ የሆኑ እና ንጹሁ ያልሆኑ ተብለው እንስሳት ለምግበ እስራኤል መለየታቸው ነው።...

የሰንበት ዕይታ - 14. የኢዮብ መጽሐፍ እንቆቅልሾች

January 20, 2024 ዊሊያም ብሌክ እንዳለው “በሞኝነቱ የጸና ሞኝ ጠቢብ ይሆናል።” “ያለጽናት አይደለም ጥሩ አማኝ፤ ጥሩ ኢአማኒም መሆን አይቻልም” እንደሚባለው ማለት ነው። አንዴ ያየኸውን ነገር አውቃለሁ...

1 opmerking


meskeremwoldmichael2
10 aug 2024

thanks stay inspired !!!

Like
  • Facebook
  • X
  • Instagram

© 2024   by Mulualem's Sixth Sense

Designed and built by Abel

bottom of page